በቻግኒ ከተማ ከ2 ሺ 600 በላይ ህገ ወጥ የክላሽ ጥይት ተያዘ፤

በቻግኒ ከተማ ከ2 ሺ 600 በላይ ህገ ወጥ የክላሽ ጥይት ተያዘ፤

በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር በቻግኒ ከተማ አስተዳደር ከ2600 በላይ ህገ ወጥ የክላሽ ጥይት ተይዟል።

‎መነሻዉን ጃዊ ወረዳ ያደረገ ታርጋ ቁጥር ኮድ 24372 አ.ማ የሆነ የህዝብ ማመላለሻ ቻግኒ ከተማ አስተዳደር ራንች ኬላ ላይ በከተማዉ የመረጃና ደህንነት ባለሙያ እንዲሁም በፀጥታ ሀይሎች በተደረገ ክትትልና ቁጥጥር 2 ሺ 694 ፍሬ ህገ ወጥ የክላሽ ጥይት በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል።

‎በከተማዉ ያለዉን ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝዉዉር ለማስቀረት የቻግኒ ከተማ የመረጃና ደህንነት ባለሙያዎች እንዲሁም አጠቃላይ የፀጥታ ሀይሎች እየሰሩት ላለዉ ስራ ከተማ አስተዳደሩ ምስጋና አቅርቧል።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Scroll to Top