‘የምርጫ ደኅንነት እና የጸጥታ ተቋማት ሚና’ መፅሐፍ ሽያጭ ለጀግኖች ማዕከል ግንባታ እንዲውል ተበርክቷል።
የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ (ዶ/ር) ‘የምርጫ ደኅንነት እና የጸጥታ ተቋማት ሚና’ በሚል ርዕስ የጻፉት መፅሐፍ ተመርቋል።
መጽሐፉ ለልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተደራሽ እንዲሆን በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞ፣ በእንግሊዝኛ እና በፈረንሳይኛ ተዘጋጅቷል።
ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ (ዶ/ር) ‘የምርጫ ደኅንነት እና የጸጥታ ተቋማት ሚና’ መፅሐፍ ሽያጭ የሚገኘው ገንዘብ ጀግኖች ማዕከል ማገገሚያ ግንባታ እንዲውል አበርክተዋል።
ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ (ዶ/ር) ለአማራ ክልል ጀግኖች ማዕከል ግንባታ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ በማድረጋቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።
የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ለመላው የክልሉ ፖሊስ ሰራዊት እንኳን ደስ አላችሁ ብሏል።











