ታማኝነቷን ያስመሰከረችው ኢንስፔክተር ሰላም

ታማኝነቷን ያስመሰከረችው ኢንስፔክተር ሰላም

በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የዝቋላ ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት መንገድ ትራፊክ ደህንነት ክፍል ኃላፊ የሆነችው ም/ኢ/ር ሰላም መኮነን ሚያዚያ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ረፋድ ላይ በባንክ ሂሳብ ቁጥሯ በስህተት 140,000/አንድ መቶ አርባ ሺ/ ብር ገቢ ሆነ።

ገንዘቡ የእሷ አለመሆኑን የተረዳችው ም/ኢ/ር ሰላም ለኃላፊዋ በስልክ ወዲያውኑ በማሳወቋ የገንዘቡ ባለቤት ሲጣራ የዝቋላ ወረዳ 01 ቀበሌ ፅፅቃ ከተማ ነዋው ደሳለኝ ኪሮስ መሆኑ ተረጋግጧል።

የዝቋላ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤትም ደሳለኝ ኪሮስን ወደ ቢሮ አስጠርቶ በአደረገው ማጣራት ገንዘቡን ለንግድ ትስስር ላለው ግለሰብ በሞባይል መተግበሪያ ሲያስተላልፍ በስህተት 140,000(አንድ መቶ አርባ ሽህ ) ማስተላለፍን ገልፆ ገንዘቡ ለጠቀሰው ግለሰብ አለመድረሱን ሲያውቅ ተጨንቆ እንደነበር ገልጿል።

ም/ኢ/ር ሰላምም የገንዘቡን ባለቤት ደሳለኝ ኬሮስ መሆኑን ከተረጋገጠ በኋላ 140,000 ብሩን የመለሰች ሲሆን ወጣት ደሳለኝ ኪሮስም ገንዘቡን በማግኘቱ አመስግኗል።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Scroll to Top